እንኳን ደስ ያላችሁ

በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የለቡ ቅርንጫፍ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ክላስተር ማዕከል ስር ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር የሚከተለውን ውጤት ማስመዝገብና ተሸላሚ መሆን ችሏል፡

1. በክላስተር ማዕከሉ ካሉ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረገ የ8ኛ ክፍል ውድድር 2ኛ መውጣት ችሏል፡፡

2. በክላስተር ማዕከሉ ካሉ የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረገ የ4ኛ ክፍል ውድድር ከ3 ትምህርት ቤቶች ጋር እኩል ውጤት በማምጣት በተደረገ የመለያ ውድድር 3ኛ መውጣት ችሏል፡፡

 

የአክሲዮን ማህበራችንን ድህረ ገፅ https://esdros.com/a/ እና የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Esdrossc ይከታተሉ፡፡