ውድ የተማሪዎቻችን ወላጆች/አሳዳጊዎች

በማስቀደም እንኳን ለ2013 ዓ.ም ትምህር ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እንላለን!

እንደሚታወቀው ትምህር ቤታችን በኮቪድ 19 አለም አቀፍ ወረርሽኝ ምክንያት የገጽ ለገጽ ትምህርት ከተዘጋበት ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም በተላይም የቴሌግራም ቻናሎችን በመክፈት በተቻለ አቅም ሁሉም ተማሪዎች ከትምህር ውጪ እንዳይሆኑና የተማሩትን እንዳይዘነጉ እገዛ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ከጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በፈረቃ ትምህርቱ እንዲቀጥል በተወሰነው መሰረት ዝግጅቶቻችንን አጠናቀን ተማሪዎቻችን ለመቀበል እየተጠባበቅን ቢሆንም የአዲስ አበባ ትምህር ቢሮ የመክፈቻው ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን አሳውቋል፡፡ በመሆኑም መማር ማስተማሩን ይበልጥ ሙሉ ለማድረግና የሚባክኑትን ጊዜያት ለማካካስ በማሰብ በተለይም ተማሪዎች ቤት በሚውሉበት ቀናት ከትምህር ተግባራት ውጪ እንዳይሆኑ ለጊዜው የቴሌግራም ቻናሎችን በመጠቀም ትምህርቱ እንደሚቀጥል እንገልጻለን፡፡ ትምህር ቤታችን በቀጠይ በቨርቹዋል የማስተማር መንገድ ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን ለመማር መስተማሩ ምቹ የሆነ ቴክኖሎጂ Learning Management System (LMS) ለማስጀመር ሙሉ ዝግጅቱን በመጠናቀቁና ወደትግበራ መገባት ላይ በመሆኑ አማረጮቹን ለመጠቀም እንድትዘጋጁ እናሳውቃለን፡፡