ለቅድመ መደበኛ ዋና መምህራን ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ
በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤቶች ለቅድመ መደበኛ ዋና መምህራን ሲሰጥ የቆየው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት ማሻሻያ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
የአክሲዮን ማህበሩ የሰው ሀብት አስተዳደር መምሪያ ስ/አስኪያጅ አቶ ታከለ በኩረ ስልጠናውን አስመልክተው እንደተናገሩት የቅድመ መደበኛ ትምህርት ተማሪዎች በሁሉም የትምህርት አይነቶች ብቁ ሆነው እንዲገኙ የመምህራንን ሁለንተናዊ አቅም መገንባት አስፈላጊና ለነገ የማይባል በመሆኑ ስልጠናው ተሰጥቷል፡፡
በቀን ለሶስት ሰዓታት ያህል የተሰጠው ይህ ስልጠና በጠቅላላ 30 ሰዐታት የፈጀ ሲሆን መምህራን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ማስቻሉን አቶ ታከለ ገልፀዋል፡፡ አክሲዮን ማህበሩ በቀጣይም መሰል ስልጠናዎችን በማዘጋጀት የመምህራንን ክህሎት የማሳደግና አቅማቸውን በማሻሻል ውጤታማ የማድረግ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚሰራ አቶ ታከለ ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ከህዳር 9 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በተሰጠው እና የመምህራንን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ክህሎት በማሻሻል ረገድ ጉልህ ሚና እንደተጫወተ በተገለፀው በዚህ ስልጠና ከአምስቱም ትምህርት ቤቶች 30 ዋና የቅድመ መደበኛ ትምህርት መምህራን ተሳትፈዋል፡፡
ስልጠናውን ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ከ’’ቲች ኢትዮጵያ’’ ጋር በመተባበር እንዳዘጋጀው ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአክሲዮን ማህበራችንን ድህረ ገፅ https://esdros.com/a/ እና የቴሌግራም ቻናል https://t.me/Esdrossc ይከታተሉ፡፡