በአቡነ ጎርጎርዮስ ስም የተከፈተው https://t.me/ABUGS ቴሌግራምአካውንት ሀሰተኛ መሆኑ ታወቀ፡፡

በአቡነ ጎርጎርዮስ ስም ሀሰተኛ የቴሌግራም ግሩፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መኖሩን የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ አስታቋል፡፡
በአቡነ ጎርጎሪዮስ ስም https://t.me/ABUGS የቴሌግራም አካውንት ሀሰተኛ እና በየትኛውም የአቡነ ጎርጎሪዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ላይ የማይታወቅ መሆኑ ታውቋል፡፡
ይህ ሀሰተኛ የቴሌግራም አካውንት የትኛውንም የአቡነ ጎርጎሪዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የማይወክል በመሆኑ አንባቢያን እንዲያውቁት እና እንድትጠነቀቁ ኩባንያችን ያሳስባል፡፡
አክስዮን ማህበራችን ይህንን ሀሰተኛ የቴለግራም አካውን በመክፈት ስለተቋሙ የተዛባ መረጃ የሚያስተላልፉትን አካላት ክትትል በማድረግ ህጋዊ እርምጃ ለማስወሰድ እየሰራ መሆኑን እያሳወቅን በዚህ ሀሰተኛ የቴሌግራም ገጽ በሚለቀቁ ሀሰተኛ መረጃዎች ኩባንያችንን የማይወክሉ መሆኑን እየገለጽን አንባቢያን የአክሲዮን ማኅበራችንን ትክክለኛ የቴሌግራም አካውንት https://t.me/EsdrosSharecopmany መሆኑን እንገልጻለን፡፡

የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገፅ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::