በ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ውጤት የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 2ኛ ወጣ

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በ2015ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች በተካሄደው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ሚኒስትሪ ፈተና ተማሪ ባሮክ ቴዎድሮስ 99.99 ውጤት በማስመዝገብ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቤቶች ሁለተኛ ወጥቷል፡፡
ከ28 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ በተዘጋጀው የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የአቧሬ ቅርንጫፍ ተማሪ የሆነው ተማሪ ባሮክ ቴዎድሮስ ከ73,667 መካከል 2ኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡
ሰኔ 28 እና 29 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብቻ በ182 የመፈተኛ ጣቢያዎች በተከናወነው የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ካሰፈተናቸው 73,667 ተማሪዎች መካከል ተማሪ ባሮክ 2ኛ መሆን ችሏል፡፡
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ይፋ በተደረገው የ6ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ውጤት ተማሪ ባሮክ ቴዎድሮስ ከአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች አቧሬ ቅርንጫፍ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ለፈተና ከቀረቡ አጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል 99.99 ያስመዘገበ ተማሪ በመሆን የ2ኛ ደረጃን ማግኘቱን ከቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

 

Abune Gorgorious