አክሲዮን ማህበሩ በነደፈው ስልት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጉዳትን መቀነስ ተችሏል

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ አጠቃላይ የተከፈለ ካፒታሉ 135 ሚሊዮን ብር መድረሱን የአክሲዮን ማህበሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አስታወቀ፡፡

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ኮቪድ 19 ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ በድርጅቱ ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ጉዳት ቀድሞ በመተንተን በተወሰደ እርምጃ ጉዳቱን መቀነስ እንደተቻለ ተገለፀ፡፡

የአክሲዮን ማህበሩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳሲ አቶ ታደሰ አሰፋ እንደገለፁት ቦርዱ ወረርሽኙ በድርጅቱ ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ጉዳት አስቀድሞ በመተንትን እና ለእያንዳንዱ ሊከሰት የሚችል ጉዳት ተገቢውን ስልት በማስቀመጥ አስቀድሞ ሰርቷል፡፡

በበርካታ ድርጅቶች ላይ የፋይናንስ ቀውስ ያስከተለው ወረርሽኙ በአክሲዮን ማህበሩ እንቅስቃሴ ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በተሰራው ስራ ሊደርስ የሚችልን ጉዳት መቀነስ መቻሉን የገለፁት አቶ ታደሰ ሁሉም ሰራተኞች የኢኮኖሚ ችግር ሳይገጥማቸው ደመወዛቸውን እያገኙ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡

 

አክሲዮን ማህበሩ ትርፋማነቱን አስቀጥሎ እና ያጋጠሙትን ችግሮች ተቋቁሞ ዛሬ ላይ መድረሱን ያወሱት አቶ ታደሰ፤ ወረርሽኙ በማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ላይ እንቅፋት መደቀኑንም አንስተዋል፡፡ተጨማሪ ት/ቤቶችን ለማስፋፋት እና ከትምህርት ዘርፉ ውጪ ባሉ የንግድ እንቅስቃሴዎች ለመግባት አክሲዮን ማህበሩ በጀመረው እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት መፍጠሩንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

ይሁን እንጂ ለችግሮች የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እና አዳዲስ ዘርፎች ላይ ለመሰማራት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አቶ ታደሰ ጨምረው ገልፀዋል፡፡

 

 

 

በድህረ ገፅ https://esdros.com/e/ ፌስቡክ https://www.facebook.com/Esdros-Construction-Trade-and-Industry-SC-282021025628947 ይከታተሉ።