አክሲዮን ማህበሩ 8ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውንና 7ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ
ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ 8ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውንና 7ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት በአዲስ አበባ ግሎባል ሆቴል አካሄደ፡፡
በጉባዔው የ8ኛ መደበኛ የጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎችን የማፅደቅ፣ አዳዲስ ባለአክሲዮኖችን የመቀበል፣ የዲሬክተሮች ቦርድ የ2012 በጀት አመት አፈፃፀም ሪፖርት ሰምቶ የማፅደቅ እና የውጪ ኦዲተር ሪፖርት የመስማትና ማፅደቅ ስራ ተከናውኗል፡፡
የአክሲዮን ማህበሩ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳሲ አቶ ታደሰ አሰፋ የ2012 በጀት አመት ሪፖርትን አቅርበው ውይይት የተደረገበት ሲሆን የበጀት አመቱ የትርፍ ክፍፍል ላይ የመወሰንን ጨምሮ የዲሬክተሮች ቦርድ አባላት አበል ማፅደቅ እና የ8ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለጉባኤ ማፅደቅ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
አክሲዮን ማህበሩ በ2013 ዓ.ም ሊሰራቸው ያቀዳቸው የትኩረት መስኮችን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዕለቱ ስብሰባው በ7ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎቹ ውስጥ የ7ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎችን ያጸደቀ ሲሆን፣ የአክሲዮን ማህበሩን ካፒታል ማሳደግ ላይ ውይይት አድርጓል፡፡
ባለአክሲዮኖችም በቀረቡ ሪፖርቶች ዙሪያ አስተያየት እና ጥያቄዎችን አንስተው ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ወደ ፊት ሊሻሻሉ በሚገባቸውና በትኩረት ሊሰራባቸው በሚገቡ የስራ ዘርፎች ዙሪያ ያላቸውን ምልከታ ገልፀዋል፡፡
በድህረ ገፅ https://esdros.com/e/ ፌስቡክ https://www.facebook.com/Esdros-Construction-Trade-and-Industry-SC-282021025628947 ይከታተሉ።