ሰሚት ቅርንጫፍ በ12ኛ ክፍል ውድድር 1ኛ ሆነ፡፡

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በበሻሌ ጉድኝት በሚገኙ የመንግሥትና የግል ትምህርት ተቋማት መካከል በተደረገ የ12ኛ ክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሰሚት ቅርንጫፍ ውድድሩን 1ኛ በመውጣት አሸንፏል፡፡
ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በተደረገው የሶሻል ሳይንስ ዲፓርትመንት የጥያቄና መልስ ውድድር ተማሪ አዶናይ ሙልጌታ ሁሉንም የቀረቡለት ጥያቄዎችን በመመለስ በሰፊ ልዩነት ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቃለች፡፡

abune Gorgorios

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በሻሌ ጉድኝት ስር በሚገኙ 6 የመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የሶሻል ሳይንስ ጥያቄዎች ሙሉ በሙሉ በመመለስ ተፎካካሪዎቹን በሰፊ ልዩነት በመምራት ተማሪ አዶናይ የወርቅ ዋንጫ እና የወርቅ መዳሊያ ተሸላሚ መሆን ችሏል ።
በሌላ መልኩ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሰሚት ቅርንጫፍ በክፍለ ከተማው በቅርቡ በተደረገ የ9ኛ የጥያቄና መልስ ውድድር ተማሪ ምሕረት አስተካከለኝ ውድድሩን በአንደኝነት በመውጣት ማሸነፏአ ይታወሳል፡፡
የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገፅ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::