ሲኤምሲ ቅርንጫፍ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 1ኛ ሆነ ፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሲኤምሲ ቅርንጫፍ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በክፍለ ከተማው 9 ወረዳዎች ከሚገኙ የመንግሥትና የግል ትምህርት ተቋማት መካከል በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 13 የሚገኙ 16 ትምህርት ቤቶችን በመወከል በክፍለ ከተማው 1ኛ በመውጣት አሸንፏል፡፡
በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ታሕሣሥ 22 ቀን 2016 ዓ.ም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት በተደረገው የጥያቄና መልስ ውድድር የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሲኤምሲ ቅርንጫፍ ተማሪ የሆነው ተማሪ ኪዳነቃል ባያብል በውድድሩ 1ኛ በመውጣት የዋንጫ ፣የሜዳሊያ ና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗል፡፡

Abune Gorgorios  

ተማሪ ኪዳነቃል ባያብል ታሕሣሥ 18 ቀን2016 ዓ.ም በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት አዳራሽ በተካሄደ የጥያቄና መልስ ውድድር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 13 ከሚገኙ 15 የመንግሥትና የግል ትምህርት ተቋማት መካከል በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሲኤምሲ ቅርንጫፍ ውድድሩን 1ኛ በመውጣት ነበር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ለሚደረገው ለአሸናፊዎች አሸነፊነት ያለፈው፡፡
በቀጣይ ተማሪ ኪዳነቃል ባያብል ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማን በመወከል በአዲስ አበባ በከተማ ደረጃ ለሚካሄደው የአሸናፊዎች አሸናፊ ይወዳደራል፡፡

Abune Gorgorios