ቃሊቲ ቅርንጫፍ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 1ኛ ሆነ ፡፡

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ቃሊቲ ቅርንጫፍ 1ኛ በመውጣት ውድድሩን አሸናፊ ሆኗል፡፡

Abune Gorgorios

በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ታህሳስ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት በተካሄደው13 ከሚሆኑ የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል በተካሄደ የጥያቄና መልስ ውድድር የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ቃሊቲ ቅርንጫፍ ተማሪ ናታን መስፍን 1ኛ በመውጣት የዋንጫ ፣የሜዳሊያና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗል፡፡
በአዲስ አበባ በከተማ ደረጃ ለሚካሄደው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ተማሪ ናታን መስፍን አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማን በመወከል ይወዳደራል፡፡

የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገፅ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::