የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሲኤምሲ ቅርንጫፍ በ1ኛነት ተሸለመ ፡፡

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 13 ትምህርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በወረዳው ከሚገኙ 15 የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት መካከል በተደረገ የጥያቄና መልስ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሲኤምሲ ቅርንጫፍ ውድድሩን 1ኛ በመውጣት አጠናቋል፡፡

Abune Gorgorios

በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል ታህሳስ 18 ቀን 2015ዓ.ም በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት አዳራሽ ባካሄደው የጥያቄና መልስ ውድድር የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሲኤምሲ ቅርንጫፍ የሆነው ተማሪ ኪዳነቃል ባያብል በውድድሩ የዋንጫ ፣የሜዳሊያና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆናለች፡፡
ተማሪ ኪዳነቃል ባያብል በቀጣይ በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚደረገው ውድድር ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13ን በስሩ የሚገኙ 15 ትምህርት ቤቶችን በመወከል ይወዳደራል፡፡
በዚሁ የጥያቄና መልስ ውድድር በ6ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል በተደረገ ወድድር ተማሪ አርሴማ እንዳወቅ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በወረዳ 13 ትምህርት ጽ/ቤት ባዘጋጀው ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ በመሆን የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆናለች፡፡