የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ወይራ ቅርንጫፍ የጥያቄና መልስ ውድድር አሸናፊ ሆነ ፡፡

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አዘጋጅነት በ9 የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት መካከል በተደረገ የ2016 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ወይራ ቅርንጫፍ ውድድሩን 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በማግኘት አሸናፊ ሆኗል፡፡
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ትምህርት ቢሮ አዘጋጅነት ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በተካሄደ የ2016ዓ.ም የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የጥያቄና መልስ ውድድር ተማሪ መክሊት አብይ እና ተማሪ ማርያማዊት አለማየሁ ከ6ኛ ክፍል ሲሳተፉ ተማሪ ያኔት ዓለምነህ እና ተማሪ ሱራፌል አያናው ከ8ኛ ክፍል በውድድሩ ተሳትፈዋል፡፡
በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ወይራ ቅርንጫፍ በ9 የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገ በዚሁ የጥያቄና መልስ ውድድር በ6ኛ ክፍል ተማሪ ማርያማዊት 2ኛ በመውጣት የሜዳሊያ ተሸላሚ ስትሆን በ8ኛ ክፍል ተማሪ ሱራፌል 3ኛ በመውጣት ከወረዳው ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል አሸናፊ ሆኗል፡፡

የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገፅ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

abune Gorgorios