የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እሑድ ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም አካሂዷል፡፡

ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ንዱስትሪ አ.ማ የዳሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር መሀሪ መኮንን አክሲዮን ማኅበሩ በ2015 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን አበይት ጉዳዮች በሪፖርታቸው ሲገልጹ፤
1. በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ከተሞች 27 ቅርንጫፍ የአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤቶች 19,014 ተማሪዎችን እያስተማረ መሆኑን፤
2. በአዲስ አበባ ከተማ 22 አካባቢ እያስገነባ ያለው ባለ 15 ወለል ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የመኖሪያ ቤት (አፓርታማ) ግንባታው 45 በመቶ መድረሱን፤
3. የ አክሲዮን ማህበሩ ዓባላት 3,585 መድረሱን እንዲሁም ኩባንያው በአሁኑ ወቅት 160 ሺህ አክሲዮን ለመሸጥ እየሰራ መሆኑን፤
4. ኩባንያው ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እንዲኖር ለማድረግ በተለይም የባለአክሲዮኖች አክሲዮን አስተዳደር መተግበሪያ (Application) አልምቶ ተግባራዊ ያደረገ መሆኑን እንዲሁም፤
5. አክሲዮን ማህበሩ በ 2015 በጀት ዓመት የነበረውን ጥቅል የፋናንስ ሪፖርት በማቅረብ በጉባኤው እንዲፀድቅ አድርገዋል፡፡

ከዚህም ሌላ ጉባኤው
 የውጭ ኦዲተር ሪፖርት በመስማት አጽድቋል፣
 የዲሬክተሮች ቦርድ የ2016 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ለጉባኤው ቀርቦ ፀድቋዋል፣
 የ2015 በጀት ዓመት የትርፍ ክፍፍል ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ተሰጥቷል፣
 ተተኪ የዲሬክተሮች ቦርድ አባልን መርጧል ፣የዲሬክተሮች ቦርድ አባላት አበል በመወሰን ስብሰባውን አጠቃሏል፡፡

 

Esdros Construction