2ኛው የ12ኛ ክፍል ኦንላይን /Online/ ፈተና ተሰጠ፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የ1ኛ መንፈቀ ዓመት አጠቃለይ ፈተናን በየቅርንጫፍ ትምህርት ቤታቸው በኦንላይ አስፈተኑ፡፡
ፈተናውን ኦንላይን /Online/ ማድረግ ያስፈለገውም መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ ፈተናው ኦንላይ ቢሆን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች እየውሰዱ ያሉት ኦንላይን ፈተና ጥሩ ተሞክሮ የሚያገኙበት እና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በሚያስችል ደረጃ መዘጋጀቱም ታውቋል፡፡

Abune Gorgorios

በአዲስ አበባ የሚገኙት የአቧሬ፣የለቡ እና የሰሚት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች የኦላየን ፈተና መፈተናቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን ፈተና ለመለማመድ የሚያስችላቸው እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡
የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ይህ የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት ማጠቃላይ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚሰጠው ብሄራዊ ፈተና ዝግጅት ተሞክሯቸውን ከማሳደጉም በላይ በራስ መተማመናቸውን በማሳደግ ውጤታማ እንዲሆኑ ያግዛቸዋል ተብሏል፡፡
በ2016 ዓ.ም መገባደጃ ላይ እንደሚሰጥ የሚጠበቀውን ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ ያሉት ቁጥራቸው 216 የሚሆኑ የአቧሬ፣የለቡ እና የሰሚት የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ይፈተናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በጥር ወር መጨረሻ ሳምንት ላይ በተካሄደው ኦንላይን /Online/ ፈተና ካለምንም የኔትወርክ መቆራረጥ ማድረግ የተቻለ መሆኑን ከኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክፍል ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Abune Gorgorios