Esdros Construction

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ ለ አመራር አካላት፣ ለርዕሳነ መምህራን እና ለዕቅድ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት በዕቅድ ዝግጅት ሂደት ላይ ሥልጠና ሰጠ፡፡

የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ ለከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮቹ እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ላይ ለሚሳተፉ የ ዕቅድ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት አጠቃላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ስልጠናው የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ የ2017 የበጀት እቅድ ወጥና ተመሳሳይ አካሄድ እንዲኖር ከቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች እስከ ዋናው መሥሪያ ቤት ተመጋጋቢና የተናበበ፣ የሚመዘን፣ ሊደረስበት የሚችል ውጤታማ የሆነ እና የግዜ ሰሌዳ የተቀመጠለት ዕቅድ ማዘጋጀት እንዲቻል ለማድረግ ታልሞ እንደሆነ ታውቋል፡፡

ስልጠናውን በ3 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ፤ የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ሂደት /“Master Budget”/ “የዕቅድ ዝግጅት ሂደት መምሰል ያለበት እና እንዴት ይዘጋጃል እንዲሁም የፊሲካል እና ፋይናሺያል ዕቅድ ግንኙነት እና ተመጋጋቢነት “key Awareness on fiscal and budget of its Correlation” በሚል ርዕስ ጉዳዮች ስልጠናዎች ተሰጥተዋል::

Esdros Construction 

የስልጠናው ተሳታፊዎች ከዚህ በፊት የነበረው የበጀት እቅድ ዝግጅት ቁልፍ ችግሮች፣ የመፍትሄ ሀሳቦች እና የ 2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጀት ምን ቅርጽ ሊኖረው ይገባል በሚሉ ርዕሳነ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡
ባለፈው ቅዳሜ መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓ.ም በተሰጠው ስልጠና ላይ 32 የሚሆኑ የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ ከፍተኛ አመራር አባላት፣ርዕሳነ መምህራን እና መካከለኛ አመራር አካላት የተሳተፉ ሲሆን ስልጠናው ለ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ዝግጅት ትልቅ ግብዓት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Esdros constructionEsdros construction

 

 

 

Esdros Construction

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና እንዱስትሪ አ.ማ በድሬደዋ አቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት የሚሰጠውን አገልግሎት እንደሚያሳድግ አስታወቀ

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና እንዱስትሪ አ.ማ በድሬደዋ አቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት ያለውን የመማር ማስተማር ሥራ የበለጠ ውጤታማ፣ ጥራቱን የጠበቀ እና አሁን ያለውን ሰፊ ፍላጎት ሊያሟላ የሚያስችለውን ተጨማሪ ክፍሎች ያሉት ደረጃውን የጠበቀ ትምህርት ቤት እንደሚከፍት አስታወቀ፡፡

Abune Gorgorios

ኩባንያችን ካሉት 27 የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ድሬደዋ ቅርንጫፍ አንዱ ሲሆን ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ ለማስፋፈት በ5034 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈውን ለመማሪያና ለአስተዳዳረር ቢሮዎች ምቹ የሆነ 40 ክፍሎች ያካተተ በመሆኑ የመቀበል አቅም በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ይጠበቃል፡፡

በዚህም በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች በድሬደዋ ቅርንጫፍ ያለውን የመቀበል አቅም ከ 980 ወደ 1600 (በ57%) ተማሪዎች በማሳደግ የወላጆችን ፍላጎት ማርካት እንደሚያስችል ከኤስድሮስ የገበያ እና ንግድ ልማት መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

 

Abungorgorios

4ኛው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የፈጠራ ሥራና ዐውደ ርእይ በታላቅ ድምቀት ተከፈተ!

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የትምህርት ዐውደ ርእይ እና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር መርሀግብር ከዛሬ አርብ መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ እሁድ መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል፡፡

Abune Gorgorious

በዚሁ ለ4ኛ ጊዜ በሚካሄደው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በኪነጥበብ፣ የተማሪ የፈጠራ ሥራ፣ ICT፣ ሥዕልና ቅርጻቅርጽ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡
በአዲስ አበባ የሚገኙት 18 የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የሚሳተፉበት ይህ አውደ ርዕይና የፈጠራ ስራዎች የሚቀርቡበት መድረክ በመርሀግብሩ ማጠቃለያ ላይ የዋንጫ፣የሜዳልያና የሰርተፍኬት ተሸላሚ እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡

Abune Gorgorios

በዐውደ ርእይ እና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር አሸናፊዎች ሽልማት ተበረከተላቸው

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የትምህርት ዐውደ ርእይ እና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር መርሐግብር ዓርብ መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ተከፍቶ ለ3 ተከታታይ ቀናት ለዕይታ በመብቃት በበርካታ እንግዶች፣ወላጆች ፣መምህራን እና ተማሪዎች ተጎብኝቷል፡፡
በዚሁ ለ4ኛ ጊዜ በተካሄደው የትምህርት ዐውደ ርእይ እና የተማሪዎች የፈጠራ ሥራ በኪነጥበብ፣ የተማሪ የፈጠራ ሥራ፣ ICT፣ ሥዕልና ቅርጻቅርጽ፣ የተቋሙ እሴት እና ዲኮረሽን (የተሰጠህን ቦታ ማሸብረቅና ማስዋብን) ዘርፍ ላይ ውድድር የተካሄድበት ሲሆን ከመጋቢት 20 እስከ 22 ቀን 2016 ዓ.ም የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 27ኛ ቅርንጫፍ በሆነው ሰንሻይን አጸደ ሕፃናትና 1ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ተካሄዷል፡፡

Abune Gorgorios

መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንተነህ ፈለቀ ናቸው፡፡ “ዘንድሮ ለ4ኛ ጊዜ የተዘጋጀው ይህ አውደ ርእይና የፈጠራ ስራዎች ውድድር የተቋሙን እሴት የሚያሳይ አዲስ የመወዳደሪያ ርእስን በማካተት ከዚህ ቀደም ከነበሩት ዝግጅቶች በተለየ መልኩ የተዘጋጀ ነው፡፡” በማለት ንግግር ያደረጉት ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ አንተነህ ፈለቀ ለዚህ ዝግጅት መሳካት አስተዋጽዖ ያደረጉትን አካላት አመስግነዋል፡፡
በመርሐግብሩ ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙት 18 ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የተሳተፉበት ሲሆን በፈጠራ ስራዎች፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በኪነጥበብ ዘርፍ በርካታ የፈጠራ ሥራዎች ቀርበው ከፍተኛ ውድድር የተካሄደባቸው ሥራዎችም ቀርበዋል፡፡
ለ3 ተከታታይ ቀናት ለእይታ በቆየው በዚህ ዐውደ ርእይ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው የኩባንያው የቦርድ እና ማኔጅመንት አመራሮች፣እንግዶች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና ተማሪዎች የጎበኙት ሲሆን የፈጠራ ስራዎችን በመዳኘት የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ባለሙያች፣ታላላቅ አርቲስቶች እና በርካታ ባለሙያዎችና ኤክስፐርቶች ተሳትፈውበታል፡፡

መጋቢት 22 ቀን 2016 ዓ.ም በመረሐ ግብሩ መዝጊያ ላይ በፈጠራ ሥራ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችና አሸናፊ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ከኤስድሮስ የዳሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ከማኔጅመንት አባላትና ከዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ከአንተነህ ፈለቀ እጅ የዋንጫ፣የሜዳሊያና የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የትምህርት ዐውደ ርእይ እና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር ከፍተኛ ፉክክር እና አስደማሚ ትዕይንቶች የታዩበት ነበር፡፡
የተቋም እሴት ላይ በተካሄደ ውድድር ከቅድመ አንደኛ በግል 1ኛ. ልዕልና መስፍን ከለቡ፣ከእግዚአብሐር አብ 2ኛ. የአብ ቴዎድሮስ እና 3ኛ. ማህሌተ ጽጌ ከሲኤምሲ ሲያሸንፉ በዚሁ ዘርፍ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በግል ከለቡ ቅርንጫፍ 1ኛ ተማሪ ህሊና ናርዶስ ፣ከቃሊቲ ቅርንጫፍ አማኑኤል ዮሐንስ እና ፍሬፅድቅ ሄኖክ 2ኛ. እና3ኛ. በመሆን አሸንፈዋል፡፡ ከሁለተኛ ደረጃ በግል፣1ኛ. ሳሮን ሳሙኤል ከአዋሬ፣ከለቡ 2ኛ. ዮሐንስ ወርቁ እና 3ኛ ቃለአብወርቁ ከቃሊቲ እሸናፊ ሆኗል፡፡
በሳይንስና ፈጠራ ዘርፍ በግል በተደረገ ውድድር ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ ከለቡ የሳይንስ መርጃ መሣሪያ በመስራት፣2ኛ ከእግዚአብሐርአብ የሂሳብ መርጃ መሣሪያ እና 3ኛ ከሲኤምሲ የቋንቋ መርጃ መሣሪያ አሸናፊ ሲሆኑ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ. ዮናታን ደጀኔ ከሰንሻይን፣2ኛ. ያፌት አብዮት ከወይራ እና 3ኛ. እነ ሶሊያና ተክላይ ከሲአምሲ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ ከ2ኛ ደረጃ በሳይንስና ፈጠራ ዘርፍም1ኛ. አናኒያ ባያብል ከሰሚት፣2ኛ. እነ ሚልካ ጫላ ከቃሊቲ እና 3ኛ ልዑል ሲሳይ ከአዋሬ አሸናፊ ሆኗል፡፡
በአይሲቲ ፈጠራ ዘርፍ በግል በተደረገ ውድድር ከአንደኛ ደረጃ 1ኛ ናሆም ሰለሞን ከእግዚአብሔርአብ፣2ኛ. ያሬድ ኤፍሬም ከለቡ እና 3ኛ. ጥበቡ ሙሉቀን ከቃሊቲ ያሸነፉ ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ. ዳግማዊ እንዳልካቸው ከአዋሬ ፣ 2ኛ በርናባስ ከለቡ እና 3ኛ. በረከት ታደሰ ከቃሊቲ በዘርፉ አሸናፉ ሆነዋል፡፡
በኪነጥበብ የፈጠራ ሥራ ዘርፍ በግል ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገ ውድድር 1ኛ ናታኔም አዲስ ከአዋሬ በመነባንብ ፣ 2ኛ. አሜን አቤል ከአዋሬ ግጥም እና 3ኛ. ሶሊያና ወልዴ ከሲ.ኤም.ሲ መነባንብ ሲያሸንፉ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ. ትምኒት አንበሴ ከለቡ መነባንብ፣2ኛ. ቤዛ ዮሐንስ ከለቡ ግጥም ፣ ተማሪ ሄርሜላ ጎሳ ከሰሚት ግጥም እና ተማሪ መክሊት ተስፋዬ ከአዋሬ እኩል 3ኛ በመውጣት በግጥም ዘርፍ አሸናፊ ሆነዋል፡፡
በሥዕልና ቅርፃቅርጽ ዘርፍ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ. እነ ሴማ ዳዊት ከሲኤምሲ 2ኛ. ተማሪ ዲቦራ ከሰንሻይን እና 3ኛ. ትንሳኤ ዳባ ከለቡ አሸናፊ ሲሆኑ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ. እነ ፍቅረማርያም ቀፀላ፣2ኛ. ሚካኤላ ያፌት ከለቡ እና 3ኛ. ጽዮን ፍሬው ከአዋሬ ሆነዋል፡፡

Abune Gorgorios

በአጠቃላይ ውጤት የተቋም እሴት ዘርፍ ላይ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ 1ኛ. ለቡ ቅርንጫፍ ፣ 2ኛ እግዚአብሔርአብ ቅርንጫፍ እና ሃያሁለት ቅርንጫፍ 3ኛ በመውጣት ሲያሸንፉ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ. ለቡ፣2ኛ ሰንሻይን እና 3ኛ አዋሬ ቅርንጫፎች አሸንፈዋል፡፡ከሁለተኛ ደረጃ1ኛ. ለቡ፣2ኛ. አዋሬ እና 3ኛ ቃሊቲ ቅርንጫፎች አሸናፊ ሆነዋል፡፡
በአጠቃላይ ውጤት በሳይንስና ፈጠራ ሥራ ውድድር ከቅድመ አንደኛ1ኛ. ሲኤምሲ፣2ኛ እግዚአብሔር አብ እና 3ኛ ለቡ ቅርፍነጫፎች አሸናፊ ሆነዋል፡፡ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሳይንስና ፈጠራ ሥራ 1ኛ. ሰንሻይን፣2ኛ. ወይራ እና 3ኛ. ሲኤምሲ ቅርንጫፍ ሲያሸንፍ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሳይንስና ፈጠራ ስራ ውድድር 1ኛ. ሰሚት፣2ኛ. ቃሊቲ እና 3ኛ. አዋሬ እና ለቡ አሸንፈዋል፡፡
በአጠቃላይ ውጤት አይሲቲ የፈጠራ ሥራ ዘርፍ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ. ቃሊቲ፣2ኛ. እግዚአብሔርአብ እና 3ኛ. ለቡ ቅርንጫፍ ደረጃን ሲይዙ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ ቃሊቲ፣ 2ኛ አዋሬ እና 3ኛ. ለቡ አሸናፊ በመሆን ተሸላሚ ሆነዋል፡፡
በአጠቃላይ ውጤት በኪነጥበብ ዘርፍ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ 1ኛ. ለቡ፣2ኛ እግዚአብሔርአብ እና 3ኛ ሲኤምሲ ቅርንጫፍ አሸናፊ ሲሆኑ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ. አዋሬ፣2ኛ. ሲኤምሲ እና 3ኛ. ሰንሻይን ቅርንጫፍ አሸናፊ በመሆን ሲያሸንፉ ከሁለተኛ ደረጃ 1ኛ. ለቡ፣2ኛ. አዋሬ እና 3ኛ. ቃሊቲ ቅርንጫፍ በዘርፉ አሸናፊነትን አግኝተዋል፡፡
በአጠቃላይ ውጤት ሥዕልና ቅርፃ ቅርፅ ዘርፍ በቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች መካከል ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1ኛ ሲኤምሲ፣2ኛ. ለቡ እና 3ኛ. ሰንሻይን ቅርንጫፎች ሲያሸንፉ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 1ኛ. ሰሚት፣2ኛ. ለቡ እና 3ኛ. አዋሬ አሸናፊ በመሆን ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

Abune Gorgorios

Abune Gorgorios

Abune Gorgorios

ለ4ኛ ጊዜ ዝግጅቱን ያስተባበረው የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ ይህን መሰል የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች የፈጠራ ሥራዎች እና የትምህርት ዐውደ ርእይ በቀጣይም ዓመት ከዚህ ዝግጅትና ቦታ በተሻለ ሁኔታ እንደሚያዘጋጅ ይጠበቃል፡፡

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

Esdros Construction

ኤስድሮስ ሪል እስቴት የመጀመሪያውን ምዕራፍ አጠናቀቀ

የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ አካል የሆነው ኤስድሮስ ሪል እስቴት 22 አካባቢ እያስገነባ የሚገኘውን ባለ 3B+G+15 ግንባታ የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆነው የእስትራክቸር ሥራ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡
የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ የግንባታና ምህንድና ዘርፍ እንዳስታወቀው የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆነው የእስትራክቸር ስራ ማጠናቀቁና በቀጣይም የህንጻውን የማጠናቀቂያ ስራዎች ለመስራት ዝግጅት መጀመሩን አስታውቋል፡፡
ባማኮን ኮንስትራክሽን በዋና ኮንትራክተርነት እና ሳይ ኮንሰልታንት ሥራውን እያፋጠኑ የሚገኙበት 68 ቤቶች ያሉት ኤስድሮስ ሪል እስቴት ስራዎቹን በተያዘላቸውና የቤቱን ገዥዎች በተዋዋሉት መሠረት ለማስረከብ እየሠራ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡

ለመኖሪያነት ምቹ በሆነው 22 አካባቢ እየተገነባ ያለው አፓርታማ ባለ 3 መኝታ ጠቅላላ ስፋታቸው 187.68 ካሬ ሜትር ፣ባለ 2 መኝታ ጠቅላላ ስፋታቸው፤ 129.48 ካ.ሜ- Type A፣131.85 ካ.ሜ Type B እና 133.04 ካ.ሜ Type C እንዲሁም ባለ 1 መኝታ ጠቅላላ ስፋታቸው 69.13 ካ.ሜ.ለገበያ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡
በአሁኑ ወቅት ከአጠቃላይ ቤቶቹ 40% ቤቶች የተሸጡ ሲሆን ዘመናዊ ሊፍት፣አውቶማቲክ ጀነሬተር ሚገጠምለት እና ደህንነቱ አስተማማኝ ጥበቃ ያለው የመኪና ማቆሚያና መጠባበቂያ ውሃ ከዘመናዊ ፓምፕ ጋር የሚገጠምለት ሲሆን በ18 ወራት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ ለገዥዎቹ ርክክብ የሚደረግ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የቤት ገዥዎች የቤቱን ዋጋ 25 በመቶ በመክፈል ውል የሚዋዋሉ ሲሆን ሥራውን በተያዘለት የጊዜ መርሀግብር ለማጠናቀቅ እና ለቤት ገዥዎች ካርታና የቤቱን ቁልፍ ለማስረከብ ግንባታው እየተፋጠነ ይገኛል፡፡

Esdros construction

Abune gorgorios

4ኛው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የፈጠራ ሥራና ዐውደ ርእይ ሊከፈት ነው!

Abuneg photo

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች የትምህርት ዐውደ ርእይ እና የፈጠራ ሥራዎች ውድድር መርሀግብር አርብ መጋቢት 20 ቀን 2016 ዓ.ም ይከፈታል፡፡
ለ4ኛ ጊዜ በሚካሄደው የትምህርት ዐውደ ርእይ እና የተማሪዎች የፈጠራ ሥራ በኪነጥበብ፣ የተማሪ የፈጠራ ሥራ፣ ICT፣ ሥዕልና ቅርጻቅርጽ፣ የተቋሙ እሴት እና ዲኮረሽን (የተሰጠህን ቦታ ማሸብረቅና ማስዋብን) ዘርፍ ላይ ውድድር የሚካሄድበት ሲሆን ከመጋቢት 20 እስከ 22 ቀን 2016 ዓ.ም የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች 27ኛ ቅርንጫፍ በሆነው ሰንሻይን አጸደ ሕፃናትና 1ኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ይካሄዳል፡፡
በመርሐግብሩ ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙት 18 ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች የሚሳተፉበት ሲሆን በፈጠራ ስራዎች፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በኪነጥበብ ዘርፍ በርካታ የፈጠራ ሥራዎች የሚቀርቡበት በመሆኑ ፉክክሩም ከፍተኛ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
ለ3 ተከታታይ ቀናት ለእይታ በሚቆየው በዚህ ዐውደ ርእይ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወላጆች፣ መምህራን እና ተማሪዎች እንደሚጎበኙት ይጠበቃል፡፡ በመሆኑም፣ እርስዎም የዐውደ ርእይው ተሳታፊ እንዲሆኑ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል፡፡

Esdros Construction

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ በልዩ ቅናሽ አክሲዮን ለሽያጭ አቀረበ

ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ በበርካታ አዳዲስ የኩባንያችን ባለአክሲዮን ለመሆን ፍላጎት ባላቸው ደንበኞቹ ጥያቄ መሰረት እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ብቻ የሚቆይ አዳዲስ አክሲዮኖችን እንደሚሸጥ ነው ያስታወቀው፡፡

ዘመኑን በዋጁ 12 ባለ አክሲዮኖች በብር 100 ሺህ ተመስርቶ በአሁኑ ወቅት ከ3750 በላይ ባለ አክሲዮኖች ያቀፈው ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ አዳዲስ አክስዮኖችን በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡

Esdros Construction

በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እና በዋናዋና የክልል ከተሞች በ27 የአቡነ ጎርጎሪዮስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ከ19 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ የሚገኘው ኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤቶች ተፈላጊነት ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ በመምጣቱ ተደራሽነቱን ለመጨመር እና ጥራት ያለው የትምህርት አገልግሎት መስጠት እንዲቻል አዲስ ት/ቤቶቹን መክፈት እና ያሉትንም ማስፋፋት ተገቢ በመሆኑ ለትምህርቱ ዘርፍ እገዛ ለማድረግ እንዲያስችለን እና አዳዲስ የቢዝነስ እሳቤዎችን ተግባራዊ ለማድረግ በተለምዶ 22 አካባቢ አክሱም ሆቴል ጀርባ 3B + G + 15 ወለል ያለው ለቅይጥ አገልግሎት የሚውል የመኖሪያ አፓርታማ በመግንባት ላይ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ግዜ የእስትራክቸራል ስራው ተጠናቋል፡፡

Esdros Construction

አክሲዮን ማኅበሩ ባለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት 29 በመቶ በዓመት ትርፍ ያስመዘገበ ከመሆኑም በላይ፣ በአሁኑ ወቅት የጠቅላላ ሀብት መጠኑን 1 ቢሊዮን ብር ያደረሰ ኩባንያ መሆኑ ተመራጭ አድርጎታል፡፡

ይህንን ተግባር የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ፣ እንዲሁም የተቋሙን ባለአክሲዮን የመሆን ፍላጎት ባላቸው በ አዳዲስ ዕጩ ባለአክሲዮኖች ጥያቄ መሰረት ቀድሞ የነበረውን ዝቅተኛ የአክሲዮን ሽያጭ መጠን ከ100 አክሲዮን ወደ 50 አክሲዮን ዝቅ ተደረጎ የአክሲዮን ሺያጭ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

በመሆኑም የአክሲዮን ጉዳዮችን በተመለከተ መረጃ ለማግኘት፣ የኩባንያውን የኮርፖሬት ማርኬቲንግ እና ንግድ ልማት መምሪያ በስ.ቁ +251 157-59-54/0930-36-37-79 /0973-60-00-10 በመደወል አክሲዮን በመግዛት የኩባንያ ባለቤት እንዲሆኑ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

Esdros Construction Esdros constructon

 

 

 

Esdros Construction

ዝቅተኛ የአክሲዮን መሸጫ

ከዚህ ቀደም መግዛት የሚቻለው ዝቅተኛው የአክሲዮን መጠን 100 አክሲዮን የነበረው በደንበኞቻችን ጥያቄ መሰረት 50 አክሲዮን እንዲሆን ተደርጓል ፡፡

 

Esdros construction

Abune Gorgorios

የሥራ አመራርና አስተዳደር ስልጠና ተሰጠ፡፡

በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን፣ ለፈረቃ አስተባባሪዎች እና ለክፍል ኃላፊዎች በሥራ አመራርና አስተዳደር ርዕሰ ጉዳዮቸ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የስልጠናው ዓላማ የትምህርቱን አስተዳደር የሚመሩ አካላት በአስተዳዳር ሥራ ላይ የሚገጥማቸውን ችግሮች መፍታት በሚያስችላቸው ክህሎት ላይ ውጤታማ በማድረግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ማቀላጠፍ የሚያስችል ተተኪዎችን ለማፍራት ያለመ እንደነበር ታውቋል፡፡

Abune Gorgorios

ስልጠናው በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ዘርፍ ያዘጋጀው ሲሆን ስልጠናውም ምክትል ሥራ አስኪያጅ የትምህርት ዘርፍ በአቶ ዘርይሁን ክብረት ፣ በአቶ መኮንን ጓዕለ የፈተናና ምዘና ክፍል ኃላፊ፣በአቶ አለሙ ወልዴ የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት አስተባባሪና በርዕስ መምህር ሙላዓለም ታደሰ የለቡ 1ኛ ደረጃ ርዕሰ መምህር አማካይኝነት ተሰጥቷል፡፡
ስልጠናው በሁለት ዙር የተካሄደ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር ስልጠና ጥር 29 እና 30 ቀን 2016 ዓ.ም በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በአቧሬ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት የተከሄደ ሲሆን ሁለተኛው ዙር ስልጠና ደግሞ የካቲት 8 እና 9 ቀን 2016 ዓ/ም በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ለቡ ቅርንጫፍ ት/ቤት ተሰጥቷል፡፡
በስልጠናው 18 ርዕሳነ መምህራን፣ 23 ም/ርዕሳነ መምህራን፣25 ፈረቃ አስተባባሪ፣61 የትምህርት ክፍልዲፓርትመንት ተጠሪዎች፣22 መምህራን፣5 ባለሙያዎች እና 6 አመራር በድምሩ 160 አካላት በስልጠናው መሳተፋቸውን ከስልጠና አስተባባሪ ዋና ክፍል ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

 

Abune Gorgorios

ሰሚት ቅርንጫፍ ከሞዴል አፍሪካ ሽልማት ተበረከተለት ፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሰሚት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሞዴል አፍሪካ ኢትዮጵያ አዘጋጅነት አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ከሚገኙ 4 ትምህርት ቤቶች ጋር አፍሪካዊ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በተደረገ የቃል ክርክር/ debate/ ላይ በመሳተፍ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ በተዘጋጀ “የ21ኛው ክፍለ ዘመን የአፍሪካ የልማት አቅጣጫ የወጣቶች ግብ በ2030” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ የክርክር መድረክ ላይ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሰሚት ቅርንጫፍ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 11 ተማሪዎች ከፍተኛ ተፎካካሪ በመሆን የተሳተፉበት እንደነብር ታውቋል፡፡
በጥር ወር መጨረሻ ሳምንት ላይ በተካሄደው አፍሪካዊ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከአዲስ አበባ የተወጣጡ 4 የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል ከፍተኛ የቃል ክርክር/debate/ በማድረጉ ሰሚት 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ሰርተፍኬ እንደተበረከተለት ከቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ሰሚት ቅርንጫፍ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ውድድሮች በመሳተፍ በርካታ ሽልማት የተበረከቱለት መሆኑ ይታወሳል፡፡
የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገፅ https://esdros.com በመከታተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

Abune Gorgorios

 

Abune Gorgorios

ለመምህራን ሥርዓተ ትምህርት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች መምህራን ሥርዓተ ትምህርቱን ውጤታማ ማድረግ በሚያስችሉ ርዕስ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
የስልጠናው ዓላማ መምህራን ሥርዓተ ትምህርቱን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል ተገቢ ክህሎት እንዲኖራቸውና የተቃና አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል ሲሆን ቁጥራቸው 86 የሚደርሱ መምህራን የተሳተፉበት በ5 ርዕሳን ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥተዋል፡፡

Abune Gorgorios

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንተነህ ፈለቀ ስልጠናውን በማስመልከት ባደረጉት ንግግር “በዚህ ስልጠና ከፍተኛ ዕውቀት እና ተሞክሮን እንዳገኛችሁበት ይታመናል፡፡ ከእናንተ ደግሞ ያገኛቹህትን ክህሎት በተግባር በማዋል ከፍተኛ ለውጥ ለማምጣት እንድትሰሩ አደራ ማለት እፈልጋለሁ” በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ከጥር 27 እስከ ጥር 30 ቀን 2016ዓ.ም ለአራት ተከታታይ ቀናት በተሰጠው ስልጠና የአሰልጣኞቹና የሰልጣኞቹ ጥምረት ከፍተኛ እንደነበር ከስልጠናው ተሳታፊዎች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡