Abune Gorgorios

ለቡ ቅርንጫፍ የጥያቄና መልስ ውድድር አሸናፊ ሆነ፡፡

በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የለቡ ቅርንጫፍ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አዘጋጅነት በተካሄደ በጠቅላላ ዕውቀት የጥያቄና መልስ ውድድር ሁለተኛ በመሆን አሸናፊ ሆኗል፡፡
በ2016ዓ.ም ለሚከበረው በሀገር አቀፍ ደረጃ 18ኛ ጊዜ የሚከበረውን የብሔር ብሔረሰቦች ቀንን እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀንን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀ የጥያቄና መልስ ውድድር እንደነበር ታውቋል፡፡

ኅዳር 13 ቀን 2016ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከከል በተዘጋጀ በጠቅላላ እውቀት ላይ መሠረት ባደረገው የጥያቄና መልስ ውድድር በክፍለ ከተማው ከሚገኙ 15 ወረዳዎች በክፍለ_ከተማ_ደረጃ በነበረው ውድድር ተማሪ ብሌን ጥላሁን 2ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆናለች፡፡
ተማሪ ብሌን ጥላሁን ህዳር 11 ቀን 2016ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በወረዳ 01 ትምህረት ጽ/ቤት በወረዳው በሚገኙ ዘጠኝ የመንግስት እና የግል ትምህርት ተቋማበአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የለቡ ቅርንጫፍ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት በ2016
ዓ.ም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በተካሄደ የጥያቄና መልስ ውድድር በወረዳ ከተማ ደረጃ አንደኛ በመውጣቱ ነበር ወደ ክፍለ ከተማ ውድድር ያቀናችው፡፡
የአክሲዮን ማኅበራችንን ድረ ገፅ https://esdros.com በመከታlተል ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ::

Abune Gorgorios

 

 

Esdros Construction

፲፩ኛው የባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ኅዳር 30 ይካሄዳል ፡፡

የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ 11ኛው የባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ለማካሄድ ዝግጅት መጀመሩን አስታወቀ፡፡
ኩባንያው 11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ እሑድ ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ በቀድሞው ግሎባል ሆቴል በአሁኑ ኢትዮጵያ ሆቴል ቁጥር ሁለት እንደሚካሄድ የዳሬክተሮች ቦርድ አስታውቋል፡፡

ጉባኤው የጠቅላላ ጉባዔ አጀንዳዎችን ማጽደቅ፣ አዳዲስ ባለ አክሲዮኖችን መቀበል፣ የዲሬክተሮች ቦርድ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ፣ የውጭ ኦዲተር ሪፖርት ፣የዳሬክተሮች ቦርድ የ2016 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎችን ፣ የዳሬክተሮች ቦርድ የ2016 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ፣የ2015 በጀት ዓመት የትርፍ ክፍፍል ላይ መወሰን፣ተተኪ የዳሬክተሮች ቦርድ አባልን ማጽደቅ፣የዳሬክተሮች ቦርድ አባላትን አበል ማጽደቅ እና የ11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ቃለ ጉባኤ ማጽደቅ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
በዚሁ ጉባኤም በ8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የ8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎችን ማጽደቅ፣የአክሲዮን ማኅበሩን መመሥረቻ ጽሑፍ ማሻሻልና ማጽደቅ እና የ8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን ማጽደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ከዳሬክተሮች ቦርድ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
በጉባኤው ላይ መገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች ጉባኤው ከመካሔዱ በፊት ሜክሲኮ ሰንጋተራ ሕብረት ባንክ ሕንፃ 8ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የአክሲዮን ማኅበሩ ቢሮ በአካል በመገኘት የውክልና ቅጽ በመሙላት ውክልና መስጠት የምትችሉ ሲሆን ተወካዮቻችሁ የውክልና ፎርሙን ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን እንዲሁም የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም የመንጃ ፈቃድ ይዘው እንዲቀርቡ በማድረግ መሳተፍ የሚችሉ መሆኑ ተገልጾል፡፡

ጉባኤው የጠቅላላ ጉባዔ አጀንዳዎችን ማጽደቅ፣ አዳዲስ ባለ አክሲዮኖችን መቀበል፣ የዲሬክተሮች ቦርድ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ፣ የውጭ ኦዲተር ሪፖርት ፣የዳሬክተሮች ቦርድ የ2016 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎችን ፣ የዳሬክተሮች ቦርድ የ2016 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ፣የ2015 በጀት ዓመት የትርፍ ክፍፍል ላይ መወሰን፣ተተኪ የዳሬክተሮች ቦርድ አባልን ማጽደቅ፣የዳሬክተሮች ቦርድ አባላትን አበል ማጽደቅ እና የ11ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ቃለ ጉባኤ ማጽደቅ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
በዚሁ ጉባኤም በ8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የ8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎችን ማጽደቅ፣የአክሲዮን ማኅበሩን መመሥረቻ ጽሑፍ ማሻሻልና ማጽደቅ እና የ8ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን ማጽደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ከዳሬክተሮች ቦርድ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
በጉባኤው ላይ መገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች ጉባኤው ከመካሔዱ በፊት ሜክሲኮ ሰንጋተራ ሕብረት ባንክ ሕንፃ 8ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የአክሲዮን ማኅበሩ ቢሮ በአካል በመገኘት የውክልና ቅጽ በመሙላት ውክልና መስጠት የምትችሉ ሲሆን ተወካዮቻችሁ የውክልና ፎርሙን ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን እንዲሁም የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም የመንጃ ፈቃድ ይዘው እንዲቀርቡ በማድረግ መሳተፍ የሚችሉ መሆኑ ተገልጾል፡፡

ስለ ጉባኤው ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ የወጣውን ማስታወቂያ መመልከት የሚቻል መሆኑ ታውቋል፡፡

ስለ ጉባኤው ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ የወጣውን ማስታወቂያ መመልከት የሚቻል መሆኑ ታውቋል፡፡

Esdros Construction

 

 

Esdros Construction

በ2015 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም እና በ2016 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ የዋና መሥሪያ ቤት ሠራተኞች በ2015ዓ.ም ዕቅድ አፋጻጸም እና በ2016ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
ጥቅምት 24 ቀን 2016ዓ.ም በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች በወይራ ቅርንጫፍ አዳራሽ በተካሄደው የ2015ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፓርት ላይ እና በ2016 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

  Esdros Construction

የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ የዕቅድ ዝግጅትና ግምገማ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ እንዳለ ተሾመ የ2015ዓ.ም አፈጻጸም እና የ2016ዓ.ም ዕቅድን ለሠራተኞች በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ረፖርትም የተማሪዎችን ቅበላና ምዝገባን በ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት በድምሩ 17,208 ተማሪዎችን ለመመዝገብ ታቅዶ 16,736 (97%) ተከናውኗል፡፡1 አዲስ ትምህርት ቤት ለመክፈት ታቅዶ የቃሊቲ ትምህርት ቤት ግዥ ተከናውኗል፡፡ 2 አዲስ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት ታቅዶ የሰንሻይን ቅድመ 1ኛ እና 1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተከፍተው ምዝገባ መከናወኑን፡፡በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ ለ1,747 ርዕሳነ መምህርን፣ ለመምህራን ለኃላፊዎች እንዲሀም ለአስተዳደር ሠራተኞች ስልጠና ለመስጠት ታቅዶ ተሠጥቷል፡፡

ለግማሽ ቀን በቆየው የ2015ዓ.ም ዕቅድና አፈጻጸም እና በ2016ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ መርሐ-ግብር ላይ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን የየስራ ክፍል ኃላፊዎችም ማብራሪያና ገለጻ አድርገዋል፡፡

 

Abune Gorgorios

ለቡ ቅርንጫፍ ለመምህራንና ተማሪዎች ስልጠና ሰጠ፡፡

በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የለቡ ቅርንጫፍ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት ለመምህራን ፣ለ6ኛ እና ለ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎች ስልጠና ተሰጠ፡፡
ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ በ2016 ዓ.ም ሚኒስትሪ ለሚፈተኑ 207 ብዛት ላላቸው 6ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችና 178 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በ5 የስልጠና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ማለትም (Attitude, Locus of Control, Personal Responsibility, Mindsets, Success Principles) ስልጠና ሰጥቷል፡፡

 

Abune Gorgorios

 

 

Abune Gorgorios

አክሲዮን ማኅበሩ ለባለሙያዎቹ እና ለርዕሳነ መምህራን ሥልጠና ሰጠ፡፡

የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ ባለሙያዎች፣ የትምህርት ኤክስፐርቶች እና ርዕሳነ መምህራን የተሳተፉበት የሁለት ቀን ስልጠና ሰጥቷል፡፡
የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ ከዲቮትድ ኮንሰልቲንግ ድርጅት ጋር በመተባበር ለተለያዩ የሥራ ክፍል ባለሙያዎች እና ለትምህርት ኤክስፐርቶች በዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል የተቋማዊ አሰራር ባህል/Corporate Culture/በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ጥቅምት 13 እና 14 ቀን 2016 ዓ.ም ለ ባለሙያዎች፣ የትምህርት ኤክስፐርቶች እንዲሁም ጥቅምት 17 እና 18 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ለርዕሳነ መምህራን ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የተለያዩ ባለሙያዎች እና የትምህርት ኤክስፐርቶች የኩብንያውን ተቋማዊ ባሕርይና የአሠራር ባህል በመረዳት ያላቸውን ዕውቀት፣ ክህሎት እና ምልከታ በመጠቀም ኩባንያውን ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያሳድጉ ያለመ ስልጠና መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንተነህ ፈለቀ እንደተናገሩት “የእኛን ተቋም ባህል የሚያውቅ አሰልጣኝ መርጠን ነው ያመጣነው፡፡ የኤስድሮስን ባህል በሚያውቅ አሰልጣኝ የተሰጠ ስልጠና ነው፡፡ የአሰልጣኞቹን ድካም ዋጋ የምትሰጡት ወደ መሬት አውርዳችሁ ልትሰሩበት ይገባል፡፡ ከተወሰነ ወራት በኋላ በስልጠናው ያመጣችሁትን ለውጥ ማየት እንፈልጋለን፣ኤስድሮስ ከላይ ጀምሮ እስከ ታች ድረስ በአንድ ዓይነት የሥራ ባህል መሥራት አለበት፡፡” በማለት መልዕክትና የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

በስልጠናው ላይ የተገኙት የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድ እና ኢንዱስትሪ አ.ማ የኮርፓሬት የሰው ሀብት አስተዳዳር መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘርሁን አድማሱ “ኤስድሮስ ስልጠናዎችን እየሰጠ ያለው በኩባንያው ውስጥ ክፍተቶች ተጠንተው (Gape Analysis) እና በእቅድና በበጀት ተደግፎ ነው፡፡ እናንተን የምናየው እንደ አሰልጣኞች አሰልጣኝ ነው፡፡ የተሰጠው ስልጠና ወደ ተግባር መቀየር ይገባል፡፡ ለዚህ ስልጠና መሳካት ላበረከቱት አካላት ሁሉ ልባዊ ምስጋናየን አቀርባለሁ፡፡”በማለት መልዕታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Esdros Construction

 

Abune Gorgorios

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ጎበኙ::

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ፣ የአዲሰ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች የእግዚአብሔር አብ ቅርንጫፍ ተማሪዎችን ጎበኙ፡፡ብፁዕነታቸው ስለ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ የኦርቶዶክሳዊ አገልግሎት እና ተጋድሎ “ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ራሳቸውን አክብረው አባትነትን፣ ሃይማኖተኝነትን፣ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስከብሩ መሆናቸውን ብዙዎች ይስማሙበታል። የታሪክ ተመራማሪ እንደመሆናቸው በዓለም አቀፋዊነት (ሉላዊነት) መዋጥ እንዳይመጣ ማንነትን ጠብቆ በዓለም መድረክ መገኘትንም አበክረው ያሳስቡ አባት ነበሩ። ሕጻናት ሰብስቦ ማሳደግ የቤተ ክርስቲያን አንዱ ዓላማ መሆኑን በተግባር አሳይተዋል ።ለተተኪው ትውልድ ትልቅ አክብሮት እና ጥንቃቄ በማሳየታቸው ይታወቃሉ። ወጣቶች በዕውቀት እንዲበለጽጉ በብዙ ደክመዋል። ዓላማቸው፣ ጽናታቸው፣ ኢትዮጵያዊ አርበኝነታቸው፣ ለአፍሪካዊነት ያላቸው ከበሬታ፣ ለወላጅ አልባ ሕጻናት ያላቸው አክብሮት ሁሌም የማይረሱ ያደርጋቸዋል።”በማለት አጠር ያለ ትምህርት ሰጥተዋል ፡፡ አያይዘውም የአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤቶች ለትውልድ እያበረከተ ስላለው አበርክቶት አንስተው አድናቆታቸውን እና ምስጋናቸውን ቅርበዋል፡፡
የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች እግዚአብሔር አብ ቅርንጫፍ ርዕሰ መምህር አቶ የአብሥራም ስለ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቱ የገለጹ ሲሆን ካለባቸው ሰፊ የቤተክርስቲያን አገልግሎት ቅድሚያ ልጆቻቸውን ለመጎብኘትና ለመባረክ በመምጣታቸው ከፍተኛ አክብሮትና ምስጋና አቅርበዋል፡፡

 Abune Gorgorios

Abune Gorgorios

በአቡነ ጎርጎርዮስ ት/ቤቶች የሥነ-ምግባር ትምህርት ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ ጥናትና ምርምር ቀረበ፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች እየሰጠ ያለው እና የት/ቤቱ ቁልፍ እሴት የሆነው የሥነ-ምግባር ትምህርት ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ የጥናትና ምርምር ሥራ በኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ የትምህርት ኤክስፐርቶች ቀርቧል፡፡
ጥቅምት 6/2016 ዓ.ም በኤስድሮስ ኮንስትራክሽ ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ መሰብሰቢያ አዳራሽ የቀረበውን የጥናትና ምርምር መርሐግብር በንግግር የከፈቱት የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ትምህርት ዘርፍ አቶ ዘሪሁን ክብረት “ይህንን መሰል ጥናትና ምርምሮች ለተቋማት በጣም ወሳኝ ናቸው፡፡ ስኬታችንንም ሆነ ክፍተታችንን የሚያሳዩ ይህን መሰልጥናቶች ተሰንደው መቀመጣቸው የተቋሙን እሴት ለማሻገር ከፍተኛ አስተዋጽደዖ ያደርጋሉ፤ በመሆኑም እንደዚህ ያሉ ጥናታዊ ሥራዎች የመሥራቱ ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡ አጥኝዎቹንም ከልብ ማመስገን እወዳለሁ::” በማለት መልዕክት አስተላልፈው እድሉን ለጥናት አቅራቢው ሰጥተዋል፡፡

Abune Gorgorios

Esdros construction

የ2015 ዓ.ም የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ውጤት ይፋ ሆነ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ከቅድመ-አንደኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ የ2015 ዓ.ም የስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ውጤት ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ ሆኗል፡፡
ጥቅምት 2 ቀን 2016 ዓ.ም በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ወይራ ቅርንጫፍ በኤስድሮስ ትምህርት ዘርፍ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምዘና ክፍል በተዘጋጀው የ2015 ዓ.ም የተቋማት ስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ግኝት ትንተና እና ውጤት ይፋ የማድረግ መርሐግብር ተካሂዷል፡፡
በመርሐግሩ ላይ የኤስድሮስ ኮንስትራክሽን ንግድና ኢንዱስትሪ አ.ማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አንተነህ ፈለቀን ጨምሮ የኩባንያው የትምህርት ኤክስፐርቶች፣ልዩ ልዩ የኩባንያው የሥራ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የየቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን እና ምክትል ርዕሳነ መምህራን ተገኝተዋል፡፡

 

Esdros Construction Esdros Construction

 

Abune Gorgorios

በአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ለቡ ቅርንጫፍ 615 ውጤት ተመዘገበ፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ለቡ ቅርንጫፍ ተማሪ የሆነው ናሆም መርሻ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና 615 በማምጣት ከቀዳሚዎች መካከል መሆን ችሏል፡፡
በ2015 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ከወሰዱ 845 ሺህ 188 ተማሪዎች ውስጥ 27 ሺህ (3.2%) ተማሪዎች ብቻ ከ50 በመቶ በላይ በማምጣት የማለፍያ ውጤት ማስመዝገባቸው ይታወሳል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ0.01 መቀነሱን ያሳያል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 649 ከ700 በተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት መስክ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲሆን በማኅበራዊ ሳይንስ ደግሞ 533 ከ600 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ በወንድ ተማሪ መመዝገቡ ይታወቃል፡፡
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 3 ሺህ 106 ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ በሆነው የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች ለቡ ቅርንጫፍ ተማሪ የሆነው ተማሪ ናሆም መርሻ ከተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ከ 700 615 በማምጣት ከፍተኛ ውጤ በማስመዝገቡ የተሰማንን ታላቅ ክብርና ደስታ እየገለጽን ለመላው የተቋሙ ማኅበረሰብ በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!! እንላለን፡:Abune Gorgorios

Abune Gorgorios

የሃዘን መግለጫ

Abune Gorgorios